am_tw/bible/other/trial.md

1.3 KiB

ምርመራ፣ ፈተና

“ምርመራ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው፣ “ማጣራትን” ወይም፣ መፈተንን ነው። አንድ ሰው በደለኛ ወይም ንጹሕ መሆኑን ለማረጋገጥ የሚደረግ የማጣራት ወይም፣ የምርመራ ተግባር ነው። ምርመራ ወይም ፈተና ለመቋቋም የሚያዳግት ሁኔታ ሲሆን፣ ለዚያ በሚሰጠው ምላሽ አንድ ሰው ለተፈለገው ነገር ተገቢ ሊሆን ወይም ላይሆንን ይችላል።

  • አንድ ሰው በደል መፈጸም አለመፈጸሙን ለማረጋገጥ ፍርድ ቤት ውስጥ የክሱን ጭብጥ መስማት ምርመራ ወይም ፍተና ይባላል። ለዚህ የሚሆኑ ሌሎች ቃሎች፣ “ማጣራት” ወይም፣ “ማመዛዘን” የተሰኙት ሊሆኑ ይችላሉ።
  • በእግዚአብሔር በማመን መዝለቅ አለመዝለቃቸውን ለማረጋገጥ ብዙዎች መፈተናቸውን ከመጽሐፍ ቅዱስ እንመለከታለን። በተለያየ ምርመራ ወይም ፈተና ውስጥ ማለፋቸው ድብደባን፣ እስራትን ሌላው ቀርቶ ለእምነታቸው መሞትን እንኳ ያካተተ ነበር።