am_tw/bible/other/tremble.md

832 B

መንቀጥቀጥ

“መንቀጥቀጥ” ከፍርሃት ወይም ከከባድ ጭንቀት የተነሣ መናወጥ ወይም፣ መንዘፍዘፍ ማለት ነው።

  • “በጣም መፍራት” ማለትም ይሆናል።
  • አንዳንዴ፣ “መንቀጥቀጥ” መሬቱን የሚያናውጥ ታላቅ ድምፅንም ያመለክታል።
  • በእግዚአብሔር ፊት ምድር እንደምትንቀጠቀጥ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። ይህም ከፍርሃት የተነሣ በምድር የሚኖሩ ሰዎች ይንቀጠቀጣሉ ወይም ምድር ሯሷ ትንቀጠቀጣለች ማለት ነው።
  • እንደ ዐውዱ አገባብ “መፍራት” ወይም፣ “እግዚአብሔርን መፍራት” ወይም፣ “መራድ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።