am_tw/bible/other/tomb.md

1.1 KiB

መቃብር፣ የቀብር ቦታ

“መቃብር” እና፣ “የቀብር ቦታ” ሰዎች የሞተውን ሰው አካል የሚያኖሩበት ስፍራ ነው።

  • አይሁድ አንዳንዴ ዋሻዎችን እንደ መቃብር ይጠቀማሉ፣ አንዳንዴ በኮረብታ አንድ ወገን ያለውን ዐለት በመፈልፈል ዋሻ ይሠራሉ።
  • አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን መቃብሩን ለመዝጋት መቃብሩ በራፍ ላይ ትልቅና ከባድ ድንጋይ ማንከባለል የተለመደ ነበር።
  • መቃብር ወይም የቀብር ቦታ አካል መሬት ውስጥ የሚቀመጥበትን ቦታ ብቻ የሚያመለክት ከሆነ ይህን ለመተርጎም፣ “ዋሻ” ወይም፣ “ኮረብታ ላይ ያለ ጉድጓድ” ማለት ይቻላል።
  • “መቃብር” የሚለው ቃል በአጠቃላይና ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ እንደ ሞት ያለ ሁኔታ ውስጥ መሆንን ወይም የሞቱ ሰዎች ነፍሶች ያሉበትን ቦታ ያመለክታል።