am_tw/bible/other/tenth.md

1.1 KiB

አሥረኛ፣ አሥራት

“አሥረኛ” ወይም፣ “አሥራት” የተሰኙት ቃሎች የአንድን ሰው ገንዘብ፣ እህል፣ የቤት እንስሳት ወይም ሌሎች ንብረቶች አንድ አሥረኛ ክፍል ያመለክታል።

  • በብሉይ ኪዳን ዘመን ለእርሱ ምስጋና እንዲሆን ካላቸው ነገር ሁሉ አንድ አሥረኛውን እንዲሰጡ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ተናግሮአል።
  • ይህ ስጦታ በካህንነትና መገናኛ ድንኳኑን ወይም ቤተ መቅደሱን በመጠበቅ እስራኤላውያንን ያገለግሉ ለነበሩ ሌዋውያን መደጎሚያ ይውላል።
  • አዲስ ኪዳን ለእግዚአብሔር አሥራት እንዲሰጥ አያዝም፤ ይሁን እንጂ ክርስቲያናዊ አገልግሎትንና ድኾችን መርጃ እንዲሆን በልግስናና በቸርነት መስጠትን አጽንዖት ይሰጣል።
  • ይህ፣ “አንድ አሥረኛ” ወይም፣ “ከአሥር አንድ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።