am_tw/bible/other/sinoffering.md

898 B

የኅጢአት መሥዋዕት

የኅጢአት መሥዋዕት ለተፈጸመው ኅጢአት ይቅርታ ለማግኘት ይቀርብ የነበረ መሥዋዕት ነበር

  • ዕብራውያን 9፥22 ኅጢአት እንዲነጻ ከተፈለገ ለተፈጸመው ኅጢአት ዋጋ የሚሆን ደም መፍሰስ እንዳለበት ይናገራል
  • በብሉይ ኪዳን ዘመን የኅጢአት መሥዋዕት የሚሆኑ እንስሳት ይቀርቡ ነበር፤ ይሁን እንጂ፣ እነዚህ መሥዋዕቶች ለዘለቄታው የኅጢአት ይቅርታን ማስገኘት ስለማይችሉ በየጊዜው መቅረብ ነበረባቸው
  • አዲስ ኪዳን እንደሚያስታውቀው ኢየሱስ የኅጢአት ፍጹም መሥዋዕት ሆነ። የእርሱ መስቀል ላይ ሞት ለአንዴና ለሁልጊዜ የኅጢአት ዋጋ ከፈለ።