am_tw/bible/other/servant.md

2.2 KiB

ባርያ፣ ባርነት

አገልጋይ በውዴታ ወይም በግዴታ ለሌላው የሚሠራ ሰው ነው። “ባርያ” የሚለው ቃል “አገልጋይ” ማለትም ይሆናል። ከዐውዱ ጋር ይበልጥ የሚስማማው የትኛው ቃል እንደሆነ ብዙ ጊዜ ምንባቡ ግልጽ ያደርጋል

  • “አገልጋይ” ማለትም ይሆናል። ከዐውዱ ጋር ይበልጥ የሚስማማው የትኛው ቃል እንደሆነ ብዙ ጊዜ ምንባቡ ግልጽ ያደርጋል
  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን አገልጋዮች ወይም ባሪያዎች በጌታቸው ቤተሰብ ውስጥ ሁነኛ ድርሻ ነበራቸው፤ ብዙዎቹም ከቤተሰቡ አባሎች ባልተለየ ሁኔታ ነበር የሚያዙት። በብሉይ ኪዳን ዘመን አንድ ሰው የሌላው ሰው የዕድሜ ልክ አገልጋይ ለመሆን ምርጫ ያደርግ ነበር።
  • ባርያ ለሚያገለግለው ጌታ እንደንብረት የሚቆጠር ሰው ነበር። ጌቶች ባርያዎቻቸውን በጥሩ ሁኔታ ሲይዙ ሌሎች ግን ይበድሏቸው ነበር።
  • በጥንት ዘመን ያለባቸውን ዕዳ ለመክፈል አንዳንድ ሰዎች በፈቃደኝነት የአበዳሪዎቻቸው ባርያዎች ይሆኑ ነበር
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አልፎ አልፎ የምናገኘው፣ “እኔ ባርያህ ነኝ” የሚለው ሐረግ የአክብሮትና የታዛዥነት ምልክት ነበር
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ የእግዚአብሔር ነቢያትና እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ሌሎች ሰዎች ብዙውን ጊዜ፣ የእርሱ፣ “ባርያ” ተብለው ይጠራሉ
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ በክርስቶስ በማመን ለእግዚአብሔር የሚታዘዙ ብዙውን ጊዜ የእርሱ፣ “አገልጋዮች” ተብለዋል። ክርስቲያኖች፣ “የጽድቅ ባርያዎች” ተብለውም ተጠርተዋል፤ ይህም አንድ አገልጋይ ለጌታው የሚሰጠውን አገልግሎት ለእግዚአብሔር ለመታዘዝ መስጠት ጋር በንጽጽር የቀረበ ተለዋጭ ዘይቤ ነው