am_tw/bible/other/scroll.md

975 B

ጥቅልል መጽሐፍ

በጥንት ዘመን ጥቅልል ከአንድ ረጅም የፓፒረስ ገጽ ወይም ከቆዳ የሚሠራ የመጽሐፍ ዓይነት ነበር። ጥቅልሉ ላይ ከተጻፈ ወይም ከተነበበ በኋላ ሰዎች ጫፉ ላይ ትንሽ በትር መሳይ ነገር በማኖር ይጠቀልሉት ነበር

  • ጥቅልሎች ሕጋዊ ሰነዶችንና ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመጻፍ ያገለግላሉ
  • አንድ ሰው ለሌላው መልእክተኛ ጥቅልል ጽሑፍ እንዲያደርስለት ከፈለገ በሰም ያሽገው ነበር። ይህም መልእክተኛው ወይም ሌላ ሰው ውስጥ ሌላ ነገር እንዳይጽፍ ወይም እንዳያነብ ለማድረግ ነበር። ጥቅልል ጽሑፉን የሚቀበለው ሰው ስሙ ወይም ማኅተሙ አለመልቀቁን በማየት ማንም እንዳልከፈተው እርግጠኛ ይሆን ነበር።