am_tw/bible/other/reward.md

887 B

ዋጋ፣ ሽልማት

ይህ ቃል የሚያመለክተው መልካምም ሆነ ክፉ አንድ ሰው ላደረገው የሚቀበለውን ነገር ነው። “ዋጋ መስጠት” የሚያመለክተው የሚገባውን ነገር ለሰው መስጠትን ነው።

  • ሽልማት አንድ ሰው መልካም በማድረግ ወይም ለእግዚአብሔር በምታዘዙ የሚቀበለውን መልካም ወይም አዎንታዊ ነገር ሊሆን ይችላል።
  • አንዳንዴ “ዋጋ” የሚለው ቃል ከመጥፎ ፀባይ የተነሣ የሚመጣውን አሉታዊ ውጤት ያመለክታል፤ ለምሳሌ፣ “ለክፉ ሥራው የሚገባውን ዋጋ” እንደሚለው በዚህ ዐውድ፣ “ዋጋ” የሚያመለክተው ቅጣትን ወይም ለክፉ ሥራ የሚገባውን አሉታዊ ውጤት ነው።