am_tw/bible/other/proud.md

1.3 KiB

ዕቡይ/ትዕቢተኛ፣ ትዕቢት፣ ኩራት፣ ኩሩ

“ትዕቢተኛ” እና፣ “ትዕቢት” ስለ ራሱ ከፍ ያለ ሐሳብ ያለውንና ከሌሎች የበለጠ እንደ ሆነ የሚያስብን ሰው ያመለክታል።

  • ብዙውን ጊዜ ትዕቢተኛ ሰው ስሕተቱን አይቀበልም። ትሑት አይደለም።
  • ትዕቢት በሌሎች መንገዶችም ለእግዚአብሔር ወዳለመታዘዝ ያደርሳል።
  • አንዳንዴ ትዕቢት ኩራት የሚል ትርጕምም አለው፤ እንዲህ ከሆነ አንድ ሰው በፈጸመው ነገር “መኩራት” ወይም ልጆቻችን ባከናወኑት ነገር “መኩራት” የሚል ቀና ትርጕም ይኖረዋል። “በሥራዬ እኮራለሁ” ከተባለ ሥራህን በሚገባ በማከናወንህ ደስ ብሎሃል ማለት ነው።
  • አንድ ሰው ትዕቢተኛ ሳይሆን በሠራው ሥራ ሊኮራ ይችላል።
  • “ትዕቢተኛ” የሚለው ቃል ሁሌም አሉታዊ ሲሆን፣ “እብሪተኛ” ወይም፣ “እምቢተኛ” ወይም “ራስን ማግዘፍ” ማለት ነው።
  • “ትዕቢት” የሚለው ስም፣ እብሪት” ወይም፣ “ኩሩ” ወይም፣ “ራሱን የሚያገዝፍ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።