1.7 KiB
1.7 KiB
ዝሙርት አዳሪነት፣ ግልሙትና
“ዝሙት አዳሪነት” ወይም፣ “ግልሙትና” ገንዘብ ለማግኘት ወይም፣ ለሃይማኖታዊ ሥርዓት የግብረ ሥጋ ግንኙነትን የሚፈጽም ሰው ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ ዝሙት አዳሪዎችና ጋለሞቶች ሴቶች ቢሆኑም፣ አንዳንዴ ወንዶችም ሊሆኑ ይችላሉ።
- “እንደ ጋለሞታ” የሚለው ፈሊጣዊ አንጋገር፣ የግብረ ሥጋ ግንኙነት በመፈጸም እንደ ጋለሞታ መኖር ማለት ነው።
- ሐሰተኛ አማልክት የሚያመልክ ወይም ጥንቆላን የሚለማመድን ሰው ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ለማመልከት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር አንዳንዴ፣ “ጋለሞታ” በሚለው ቃል ይጠቀማል።
- ለአንድ ነገር፣ “ራስን ጋለሞታ ማድረግ” ግብረ ሥጋ መፈጠም ማለት ሲሆን፣ በምሳሌያዊ አንጋገር ጥቅም ላይ ከዋለ ሐሰተኛ አማልክትን በማምለክት ለእግዚአብሔር ታማኝ አለምሆን ማለት ነው።
- በጥንት ዘመን አንዳንድ የአረማውያን መቅደሶች የሃይማኖት ሥርዐትን ለመፈጸም በሴቶችና በወንዶች ጋለሞታዎች ይጠቀሙ ነበር።
- ይህ ቃል፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕም የሚሠራለት ቋንቋ እንዲህ ያለውን ሰው ለማመልከት በሚጠቀምበት ቃል ወይም ሐረግ መተርጎም ይችላል። አንዳድን ቋንቋዎች ይህን ለማመልከት ቀጥተኛ ያልሆነ ቃል ይጠቀሙ ይሆናል።