am_tw/bible/other/prostitute.md

1.7 KiB

ዝሙርት አዳሪነት፣ ግልሙትና

“ዝሙት አዳሪነት” ወይም፣ “ግልሙትና” ገንዘብ ለማግኘት ወይም፣ ለሃይማኖታዊ ሥርዓት የግብረ ሥጋ ግንኙነትን የሚፈጽም ሰው ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ ዝሙት አዳሪዎችና ጋለሞቶች ሴቶች ቢሆኑም፣ አንዳንዴ ወንዶችም ሊሆኑ ይችላሉ።

  • “እንደ ጋለሞታ” የሚለው ፈሊጣዊ አንጋገር፣ የግብረ ሥጋ ግንኙነት በመፈጸም እንደ ጋለሞታ መኖር ማለት ነው።
  • ሐሰተኛ አማልክት የሚያመልክ ወይም ጥንቆላን የሚለማመድን ሰው ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ለማመልከት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር አንዳንዴ፣ “ጋለሞታ” በሚለው ቃል ይጠቀማል።
  • ለአንድ ነገር፣ “ራስን ጋለሞታ ማድረግ” ግብረ ሥጋ መፈጠም ማለት ሲሆን፣ በምሳሌያዊ አንጋገር ጥቅም ላይ ከዋለ ሐሰተኛ አማልክትን በማምለክት ለእግዚአብሔር ታማኝ አለምሆን ማለት ነው።
  • በጥንት ዘመን አንዳንድ የአረማውያን መቅደሶች የሃይማኖት ሥርዐትን ለመፈጸም በሴቶችና በወንዶች ጋለሞታዎች ይጠቀሙ ነበር።
  • ይህ ቃል፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕም የሚሠራለት ቋንቋ እንዲህ ያለውን ሰው ለማመልከት በሚጠቀምበት ቃል ወይም ሐረግ መተርጎም ይችላል። አንዳድን ቋንቋዎች ይህን ለማመልከት ቀጥተኛ ያልሆነ ቃል ይጠቀሙ ይሆናል።