am_tw/bible/other/profit.md

1.5 KiB

ጥቅም፣ ጠቃሚ

በአጠቃላይ “ጠቃሚ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የሚገኝ መልካም ነገርን ነው። ለራሱ መልካምነገር የሚያስገኝ ወይም ለሌሎች መልካም ነገር የሚያስገኝ ከሆነ አንድ ነገር ጠቃሚ ነው ይባላል።

  • የበለጠ ግልጽ በሆነ መልኩ፣ ብዙውን ጊዜ፣ “ጠቃሚ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንድን ሥራ ሠርቶ የሚገኝ ገንዘብን ነው። ከወጪው የበለጠ ገንዘብ የሚያስገኝ ሥራ “ጠቃሚ” ነው።
  • ከሚያስፈልገው በላይ ገንዘብ በመጠየቅ የሚገኝ ጥቅምን መጽሐፍ ቅዱስ ይቃወማል።
  • የምጽሐፍ ቃል ሰዎችን በጽድቅ ለመምከርና ለማስተማር “ጠቃሚ” መሆኑን 2ጢሞቴዎስ 3፡16 ይናገራል። ይህም ማለት የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶች ሰዎች እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንዲኖሩ ለማስተማር ይረዳሉ፣ ይጠቅማሉ ማለት ነው።
  • 1ቆሮንቶስ 10፡23 ለክርስቲያኖች ሁሉም የተፈቀደ ቢሆንም፣ ሁሉም፣ “ጠቃሚ” እንዳልሆነ ይናገራል። ይህም ማለት አንድ ነገር የተፈቀደ ቢሆን እንኳ፣ ክርስቲያን እግዚአብሔርን ደስ በሚያሰኝ ሁኔታ እንዲኖር በመርዳት ረገድ የሚሰጠው ጥቅም የለም ማለት ነው።