am_tw/bible/other/possess.md

1.5 KiB

ንብረት ማድረግ፣ ንብረት

“ንብረት ማድረግ” እና፣ “ንብረት” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክቱት የአንዳች ነገር ባለቤት መሆንን ነው። አንድን ነገር ወይም አካባቢን መቆጣጠርንም ያመለክታል። አብዛኛውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉት በዚህ መልክ ነው።

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ይህ ቃል ብዙውን ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው፣ የተወሰነ ቦታን፣ “መያዝ” ወይም፣ “መውሰድን” በሚያመለክት ዐውድ ውስጥ ነው።
  • ምድረ ከነዓንን፣ “ንብረት” እንዲያደርጉ ያህዌ ለእስራኤላውያን ሲናገር ወደዚያ ሄደው በምድሩ መኖር አለባቸው ማለት ነው። ይህም በመጀመሪያ እዚያ ይኖሩ የነበሩ ከነዓናውያንን ድል ማድረግን ይጨምራል።
  • ምድረ ከነዓን፣ “ንብረታቸው” እንዲሆን እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ተናግሯል፤ ይህም ማለት ከነዓናውያንን ድል በማድረግ ምድሪቱን እንዲይዙ እርሱ ይረዳቸዋል ማለት ነው፥
  • የእስራኤል ሕዝብ የያህዌ፣ “የተለዩ ንብረት ወይም ርስት” ተብለዋል። ይህም ማለት እርሱን እንዲያመልኩና በእርሱ እንዲገዙ እንደ ሕዝብ የእርሱ ሆነዋል ማለት ነው።