am_tw/bible/other/neighbor.md

1.2 KiB

ጎረቤት

አብዛኛውን ጊዜ ጎረቤት የሚባለው በአካባቢው የሚኖር ሰው ነው። ይበልጥ አጠቃላይ በሆነ መልኩ፣ በምትኖሩበት ማኅበረ ሰብ ወይም የሰዎች ስብስብ ውስጥ የሚኖር ሰውን ያመለክታል።

  • “ጎረቤት” የሚለው አንዱ ትርጕም፣ እናንተ በምትኖሩበት ማኅበረ ሰብ ውስጥ የሚኖር በመሆኑ ከለላ የምትሆኑትና ደግ የምትሆኑለት ሰው ማለት ነው።
  • ስለ መልካሙ ሳምራዊ አዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስ በተናገረው ምሳሌ ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ፣ “ጎረቤት” የሚለውን ቃል የተጠቀመበት ሌላው ቀርቶ ጠላት የሚባለው እንኳ ሳይቀር የሰው ልጅን ሁሉ በሚያካትት ሰፋ ባለ ሁኔታ ነው።
  • የአሥሩ ትእዛዞች የመጨረሻዎቹ ስድስቱ ሌሎች ሰዎችን ማለትም ጎረቤቶችን መውደድ ላይ ያተኵራሉ።
  • የሚቻል ከሆነ ይህን ቃል በቃል ለመረርጎም “አጠገብህ የሚኖር ሰው” የሚል ትርጕም ባለው ቃል ወይም ሐረግ መጠቀሙ የተሻለ ነው።