am_tw/bible/other/mock.md

959 B

ማፌዝ፣ መቀለድ፣ መዘበት።

“ማፌዝ” “መቀለድና” እና፣ “መዘበት” የተባሉት ቃሎች ሁሉ የሚያመለክቱት በሚጎዳ መልኩ ሌሎችን መሳቂያ መሳለቂያ ማድረግን ነው።

  • ማፌዝ እነርሱን ለማሳፈር ወይም ንቀንትን ለማሳየት ሲባል የሰዎችን ቃልና እንቅስቃሴ አስመስሎ መነርና መንቀሳቀስንም ይጨምራል።
  • ቀይ ልብስ ሲያለብሱትና እንደ ንጉሥ እያከበሩት እንደ ሆነ ሲያስመስሉ የሮም ወታደሮች ኢየሱስ ላይ እየቀለዱ ነበር።
  • ከራሱ መላጣነት የተነሣ የተወሰኑ ወጣቶች ኤልሳዕ ላይ ቀልደውና አፊዘው ነበር።
  • “መዘበት” የሚታመን ወይም ጠቃሚ ተደርጎ በማይገመት ሐሳብ ላይ መቀለድና ማፌዝን ያመለክታል።