am_tw/bible/other/magnify.md

853 B

ትልቅ ማድረግ፣ ማጉላት

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ትልቅ ማድረግ” ታዋቂነት እንዲያገኝ በማሰብ ወደ አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር የሌሎችን ትኵረት መሳብ ማለት ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ትልቅ ማድረግ” ሲባል ሁሌም ጥቅም ላይ የሚውለው ንጉሥን ወይም ራሱ እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ ለማድረግ ነው።
  • አንድ ሰው ራሱን ትልቅ ካደረገ ያ ሰው ትዕቢተኛ ነው፤ በጣም አስፈላጊ ሰው ሆኖ ለመታየት እየሞከረ ነው ማለት ነው። በመጨረሻው ዘመን ሰዎች እንዲያመልኩት ራሱን በጣም ትልቅ የሚያደርግ ንጉሥ እንደሚመጣ ነቢዩ ዳንኤል ይናገራል።