am_tw/bible/other/lordgod.md

1.5 KiB

ጌታ

ጌታ የሚለው ቃል ሰዎች ላይ ባለቤትነት ወይም ሥልጣን ያለውን ሰው ያመለክታል።

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ይህ ቃል፣ “ሁሉን ቻይ ጌታ እግዚአብሔር” ወይም፣ “ጌታ ያህዌ” ወይም፣ “ያህዌ የእኛ ጌታ” በተሰኙት አገላለጾች ጥቅም ላይ ይውል ነበር።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ሐዋርያቱ፣ “ጌታ ኢየሱስ” እና፣ “ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ” ለማለት በዚህ ቃል ተጠቅመዋል፤ ይህም የሚያመለክተው ኢየሱስ እግዚአብሔር መሆኑን ነው።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ፣ “ጌታ” የሚለው ቃል በተለይ ከብሉይ ኪዳን በተወሰዱ ጥቅሶች በቀጥታ እግዚአብሔርን ብቻ ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል። ለምሳሌ ያህል፣ የብሉይ ኪዳን “በያህዌ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው” ሲል፣ አዲስ ኪዳን ደግሞ “በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው” ይላል።
  • ULB እና UDB ውስጥ፣ “ጌታ” የሚለው መጠሪያ ጥቅም ላይ የዋለው የዕብራይስጥም ሆነ የግሪኩ ቃል፣ “ጌታ” ለማለት በተጠቀመበት መልኩ ለመተርጎም ነው። በብዙ የተለያዩ ቦታዎች እንደ ተደረገው እንደ የእግዚአብሔር ስም (ያህዌ) ትርጕም አይደለም ጥቅም ላይ የዋለው።