am_tw/bible/other/loins.md

1.4 KiB

ወገብ

ወገብ በታችኛው ጎድንና በዳሌ አጥንት መካከል የሚገኝ የሰው ወይም የእንስሳ አካል ክፍል ነው፣ አንዳንዴ ታችኛው የሆድ ዕቃም ይባላል።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ምሳሌያዊ ወይም ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ የወንድን የመራቢያ አካል ያመለክታል፤ ምክንያቱም የወደ ፊት ዘሮቹ መገኛ ቦታ በመሆኑ ነው።
  • “ወገብን መታጠቅ” የሚለው ፈሊጣዊ ገለጻ ለከባድ ሥራ መዘጋጀትን ነው የሚያመለክተው። ይህ አባባል የመጣው አንድ ሰው ያለ ምንም ችግር መሄድ ሲፈልግ ታችኛውን የቀሚሱን ጫፍ ወገቡ ላይ ወዳለው ቀበቶ ሥር ሸጥ ያደርግ ከነበረበት ሁኔታ ነው።
  • ወገብ የብርታት ምንጭ መሆኑ ተነግሯል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥብዙ ጊዜ “ወገብ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ለመሥዋዕት የቀረበውን እንስሳ ታችኛውን የጀርባውን ክፍል ነው።
  • “ከወገብህ የሚገኘው” የሚለው ሐረግ፣ “ዘርህ ይሆናል” ወይም፣ “ከዘርህ ይወለዳል” ወይም፣ “እግዚአብሔር ከአንተ እንዲገኝ ያደርጋል” ተብሎ መተርጎም ይችላል።