am_tw/bible/other/learnedmen.md

1.3 KiB

የተማሩ ሰዎች፣ ኮኮብ ቆጣሪዎች

ማቴዎስ በሚያቀርበው የክርስቶስ ልደት ታሪክ መሠረት እነዚህ፣ “የተማሩ” ወይም፣ “ያወቁ” ሰዎች ኢየሱስ በቤተ ልሔም በተወለደ ጊዜ እዚያ ድረስ ስጦታዎች ያመጡለት “ጠቢብባን ሰዎች” ነበር። ምናልባትም ከዋክብትን የሚያጠኑ ኮከብ ቆጣሪዎች ለሆኑ ይችላሉ።

  • እነዚህ ሰዎች ከእስራኤል በስተ ምሥራቅ በጣም ርቆ ካለ አገር ነበር የመጡት። ከየት እንደ መጡና እነርሱም እነማን እነደ ሆኑ በትክክል አይታወቅም። ይሁን እንጂ፣ ከዋክብትን ያጠኑ ምሁራን መሆናቸው ግልጽ ነው።
  • ምናልባትም ከዋክብትንና ማጥናትና ሕልምን መተርጎምን ጨምሮ ብዙ ሥልጠና የነበራቸው በዳንኤል ዘመን የባቢሎን ንጉሦችን ያገለግሉ የነበሩ ጠቢባን ዘሮች ሊሆኑ ይችላሉ።
  • ለኢየሱስ የመጡት ስጦታዎች ሦስት ከመሆናቸው የተነሣ እነዚያ ጠቢባን ሦስት ሰዎች እንደ ሆኑ ይታሰባል። ይሁን እንጂ፣ ከዚያ በላይ ሊሆኑ እንደሚችሉም በጣም ግልጽነው።