am_tw/bible/other/drunk.md

870 B

መስከር፣ ሰካራም

መስከር የአልኮል መጠጥ አብዝቶ በመጠጣት አእምሮን መሳት ወይም ከተለመደው የተለየ ፀባይ ማሳየት ማለት ነው።

  • ሰካራም የሚባለው ብዙ ጊዜ የሚሰክር ሰው ነው። እንዲህ ያለው ሰው፣ “እልኮሊክ” ተብሎም ይጠራል።
  • አማኞች መንፈስ ቅዱስ እንዲገዛቸው እንጂ፣ መስከር እንደሌለባቸው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ መስከር ሞኝነት መሆኑንና ወደ ሌሎች ኃጢአቶችም እንደሚመራ ይናገራል።
  • መስከር የሚለውን ለመተርጎም ሌሎች መንገዶች፣ “መጠት ማብዛት” ወይም፣ “ከልክ በላይ መጠጣት” የተሰኙት ሊሆኑ ይችላሉ።