am_tw/bible/other/drinkoffering.md

938 B

የመጠጥ ቍርባን

የመጠጥ ቍርባን ወይን ጠጅ መሠዊያ ላይ ማፍሰስን የሚያካትት ለእግዚአብሔር የሚቀርብ መሥዋዕት ነው። ብዙውን ጊዜ የሚቀርበው ከሚቃጠል መሥዋዕትና ከእህል መሥዋዕት ጋር በአንድነት ነው።

  • የእርሱ ሕይወት እንድ መጠጥ መሥዋዕት እንደሚፈስ ጳውሎስ ተናግሮአል። ይህም ማለት መከራ ቢደርስበትም ምናልባት ከዚያ የተነሣ ሊገደል ቢችልም እግዚአብሔርን ለማገልገልና ለሰዎችም ስለ ኢየሱስ ለመናገር ሙሉ በሙሉ ሕይወቱን ሰጥቷል ማለት ነው።
  • የኢየሱስ መስቀል ላይ ሞት የመጨረሻው የመጠጥ ቍርባን ነበር፤ ምክንያቱም የእርሱ ደም ለእኛ ኃጢአት መስቀል ላይ ፈስሶአል።