am_tw/bible/other/disperse.md

1.1 KiB

መበታተን፣ የተበተነ

መበታተን የሰዎችን ወይም የነገሮችን በተለያዩ አቅጣጫ መበታተን ያመለክታል።

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ እርስ በርስ ተራርቀው በተለያየ ቦታ እንዲኖሩ ለማድረግ እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደሚበትን ይናገራል። እንዲህ የሚያደርገው በኀጢአታቸው እነርሱን ለመቅጣት ነው። ተራርቀውና ተለያይተው መኖራቸው በንስሐ እንዲመለሱና እንደ ገና እግዚአብሔርን ማምለክ እንዲጀምሩ ሊያደርጋቸው ይችላል።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ መበታተን የሚለው ቃል የሚያመለክተው ስደትን ለማምለጥ ቤታቸውን ትተው ወደ ተለያዩ ቦታዎች የሄዱ ክርስቲያኖችን ነው።
  • የተበተኑ የሚለውን፣ “በተለያዩ ቦታ ያሉ አማኞች” ወይም፣ “ወደ ተለያዩ አገሮች የሄዱ ሰዎች” ብሎ መተርጎም ይቻላል።