am_tw/bible/other/deliverer.md

1.0 KiB

መታደግ፣ ታዳጊ (የሚታደግ)

አንድን ሰው መታደግ እርሱን ማዳን ማለት ነው። ታዳጊ ከባርነት፣ ከጭቆና ወይም ከሌላ አደጋ ሰዎችን የሚታደግ ወይም ነጻ የሚያወጣ ነው።

  • በብሉይ ኪዳን ዘመን እነርሱን ለማጥቃት በመጡ ሌሎች ላይ እንዲዘምቱ በማድረግ እስራኤልን የሚጠብቁና የሚመሩ ታዳጊዎች እግዚአብሔር አስነሥቶ ነበር።
  • እነዚህ ታዳጊዎች፣ “መሳፍንት” ተብለውም ይጠሩ ነበር፤ ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለው መጽሐፈ መስፍንት እነዚህ መሳፍንቶች እስራኤልን የመሩት መቼ እንደ ነበር በዝርዝር አስፍሮአል።
  • እግዚአብሔርም፣ “ታዳጊ” ተብሎአል። ከእስራኤል ታሪክ በሙሉ እንደምንመለከተው እርሱን ሕዝቡን ከጠላቶቻቸው ታድጎአቸው ወይም አድኖአቸው ነበር።