am_tw/bible/other/declare.md

1.0 KiB

ማወጅ፣ ዐዋጅ

“ማወጅ” እና “ዐዋጅ” የተሰኙት ቃሎች የሚያመለክቱት ሰው ሁሉ እንዲያውቀው ተፈልጎ በግልጽ በአደባባይ ለሕዝብ የሚነገር ሲሆን፣ እንዲህ የሚደረገው ለጉዳዩ አጽንዖት ለመስጠት ታስቦ ነው።

  • “ዐዋጅ” ለተነገረው አጽንዖት መስጠት ብቻ ሳይሆን፣ ዐዋጁን ለተናገረ ሰው ትኵረት ውስጥ ያስገባል።
  • ለምሳሌ በብሉይ ኪዳን ዘመን ብዙውን ጊዜ ከእግዚአብሔር የመጣ መልእክት፣ “የያህዌ ዐዋጅ” ወይም፣ “ያህዌ እንዲህ በማለት ያውጃል” የሚል መቅድመ ነገር ይሰጠው ነበር። ይህ አባባል እየተናገር ያለው ያህዌ ለመሆኑ አጽንዖት ይሰጣል። መልእክቱ የመጣው ከያህዌ መሆኑ ምን ያህል አስፈላጊ ወይም ጠቃሚ መሆኑን ያመለክታል።