am_tw/bible/other/creature.md

924 B

ፍጡር

“ፍጡር” ሰዎችንና እንስሳትን ጨምሮ እግዚአብሔር የፈጠረውን ሕያው ነገር ሁሉ ያመለክታል።

  • ነቢዩ ሕዝቅኤል በራእይ የእግዚአብሔርን ክብር ሲያይ አራት፣ “ሕያዋን ፍጡራን” ማየቱን ይናገራል። በትክክል ምንነታቸውን መረዳት ባለ መቻሉ ነበር ይህን ስም የሰጣቸው።
  • ሕይወት ያላቸውንና ሕይወት የሌላቸውን ነገሮች (መሬትን፣ ባሕርንና ከዋክብትን) ጨምሮ እግዚአብሔር የፈጠራቸው የተለያዩ ነገሮችን ስለሚያካትት፣ “ፍጥረት” የሚለው ቃል የተለየ ትርጕም ሊኖረው እንደሚችል ልብ ማድረግ ይኖርብናል። “ፍጡር” ሕይወት ያላቸው ነገሮችን ብቻ ነው የሚያመለክተው።