am_tw/bible/other/confidence.md

1.5 KiB

እምነት፣ መተማመን

“እምነት” እኛ “መተማመን” አንድ ነገር እውነት መሆኑንና ያም ነገር በእርግጥ የሚፈጸም መሆኑን እርግጠኛ መሆንን ያመለክታሉ። በድፍረትና በልበ ሙሉነት መንቀሳቀስንም ያመለክታሉ።

  • እርሱ እንደማይዋሽና ምንጊዜም ቃሉን እንደሚጠብቅ በማወቃቸው እግዚአብሔርን በሰጣቸው የተስፋ ቃሎች አማኞች እርግጠኞች ናቸው።
  • እርግጠኝነት መሠረት የሚያደርገው አስቸጋሪ ሁኔታዎች ቢኖሩ እንኳ በእግዚአብሔር መተማመን ላይ ነው።
  • ሌሎች የመጸሐፍ ቅዱስ ትርጕሞች፣ “ተስፋ” በማለት የተረጎመበትን አንዳንድ ትርጕሞች፣ “እርግጠኝነት” ብለውታል፤ ይህም ያ ነገር እንደሚፈጸም በሚገባ ማወቅን ግምት ውስጥ በማስገባት ነው።
  • ብዙውን ጊዜ፣ “እምነት” የሚያመለክተው በተለይ የእግዚአብሔርን ተስፋ ቃል እውነተኛነትን፣ አንድ ቀን አማኞች ሁሉ ለዘላለም በሰማይ ከእግዚአብሔር ጋር እንደሚሆኑ እርግጠኛ መሆንን ያመለክታል።
  • “በእግዚአብሔር ማመን” እርሱ ቃል የገባውን ለመቀበልና ለመለማመድ በፍጹም ልብ መጠበቅ ማለት ነው።