am_tw/bible/other/citizen.md

1.2 KiB

ዜጋ

አንድ ዜጋ በአንድ የተወሰነ አገር ወይም መንግሥት ውስጥ የሚኖር ሰው ነው። በተለይም የዚያ አገር ነዋሪ መሆኑን በልጽ ዕውቅና የተሰጠው ሰውን ያመለክታል።

  • እንደ ዐውዱ ሁኔታ ይህ፣ “ነዋሪ” ወይም፣ “ሕጋዊ ኗሪ” ተብሎ መተርጎም ይችላል።
  • አንድ ዜጋ የአንድ ትልቅ አገር ክፍል በሆነ አገር በንጉሥ፣ በፕሬዚደንት ወይም ጠቅላይ ሚኒስትር የሚተዳደር አገር ውስጥ መኖር ይችላል። ለምሳሌ ጳውሎስ ብዙ የተለያዩ አውራጃዎች በውስጡ የያዘው የሮም መንግሥት ዜጋ ነበር፤ ጳውሎስ ከእነዚህ አውራጃዎች በአንዱ ይኖር ነበር።
  • በምሳሌያዊ አነጋገር በኢየሱስ የሚያምኑ ሰዎች የመንግሥተ ሰማይ፣ “ዜጋ” ተብለዋል፤ ይህ የሚያሳየው አንድ ቀን እዚያ የሚኖሩ መሆኑን ነው። እንደ አንድ አገር ዜጋ ሁሉ ክርስቲያኖች የእግዚአብሔር መንግሥት ዜጎች ናቸው።