am_tw/bible/other/chronicles.md

1.1 KiB

ዜና መዋዕል

“ዜና መዋዕል” የሚለው ቃል በዘመናት ውስጥ በጽሑፍ የሰፈረ ሰነድን ነው።

  • ሁለት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት፣ “1ዜና መዋዕል” እና “2ዜና መዋዕል” ተብለው ተጠርተዋል።
  • “ዜና መዋዕሎች” የተባሉት መጻሕፍት ከአዳም አንሥቶ የሰዎችን ስም በመዘርዘር የእስራኤልን ሕዝብ ታሪክ በከፊል አስፍረዋል።
  • “1ዜና መዋዕል” የንጉሥ ሳኦልን ፍጻሜና በንጉሥ ዳዊት አገዛዝ ዘመን የተከናወኑ ሁኔታዎች አስፍሮአል።
  • “2ዜና መዋዕል” የቤተ መቅደሱ መሠራትንና የሰሜኑ የእስራኤል መንግሥት ከደቡብ የይሁዳ መንግሥት መከፈሉን ጨምሮ የንጉሥ ሰሎሞንንና የበርካታ ሌሎች ነገሥታት አገዛዝ አስፍሮአል።
  • 2ዜና መዋዕል የሚያበቃው የባቢሎን ምርኮ መጀመሩን በመግለጽ ነው።