am_tw/bible/other/cherubim.md

1.5 KiB

ኪሩቤል፣ ኪሩብ

“ኪሩብ” እና “ኪሩቤል” በመባል በብዙ ቊጥር የሚጠሩት እግዚአብሔር የፈጠራቸው የተለዩ ዓይነት ሰማያዊ አካሎች ናቸው። ኪሩቤል ክንፎችና የእሳት ነበልባል እንዳላቸው መጽሐፍ ቅዱስ ያመለክታል።

  • ኪሩቤል የእግዚአብሔርን ክብርና ኃይል ይገልጣሉ፤ የተቀደሱ ነገሮች ጠባቂዎችም ይመስላሉ።
  • አዳምና ሔዋን ኃጢአት ካደረጉ በኋላ፣ ሰዎች ወደ ሕይወት ዛፍ እንዳይደርሱ የእሳት ነበልባል የሆነ ሰይፍ ያላቸው ኪሩቤልን ከገነት አትክልት ቦታ አኖረ።
  • ፊት ለፊት የቆሙና የኪዳኑ ታቦት፣ የስርየት መክደኛ ላይ ክንፎቻቸውን ያጋጠሙ ሁለት ኪሩቤል እንዲሠሩ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዘዘ።
  • መገናኛው ድንኳን ውስጥ የነበሩ መጋረጃዎችም ላይ የኪሩቤልን ምስል በጥልፍ እንዲሠሩም ነግሮአችዋል።
  • አንዳንድ ምንባቦች ውስጥ እነዚህ ፍጥረቶች አራት ፊቶች ማለትም የሰው፣ የአንበሳ፣ የበሬ እና የንስር ፌት እንዳላቸው ተገልጿል።
  • አንዳንዴ ኪሩቤል መላእክት እንደ ሆነ ይታሰባል፤ መጽሐፍ ቅዱስ ግን ያንን በግልጽ አይናገርም።