am_tw/bible/other/captive.md

1.3 KiB

ምርኮኛ፣ ምርኮ

“ምርኮና” እና፣ “ምርኮ” የተሰኙ ቃሎች መኖር በማይፈልጉበት የባዕድ አገር እንዲኖሩ ሰዎችን መያዝ ወይም ማስገደድን ያመለክታሉ።

  • ከይሁዳ መንግሥት የነበሩ እስራኤላውያን ለ70 ዓመት የባቢሎን መንግሥት ምርኮኞች ሆነው ነበር።
  • ዳንኤልና ነህምያ ለባቢሎን ንጉሥ ይሠሩ የነበሩ እስራኤላዊ ምርኮኞች ነበሩ።
  • “ምርኮኛ መሆን” የተሰኘው ፈሊጣዊ አነጋገር ሌላውን ወገን መያዝን የሚያመልክት ሌላ አባባል ነው።
  • “ምርኮኛ ትሆናላችሁ” የሚለው አባባል፣ “እንደ ምርኮኛ ለመኖር ትገደዳላችሁ” ወይም፣ “እስረኞች ሆናችሁ ወደ ሌላ አገር ትወሰዳላችሁ” ተብሎ መተርጎም ይችላል።
  • ሐዋርያው ጳውሎስ ማንኛውንም ዐሳብ፣ “መማረክና” ለክርስቶስ እንዲታዘዝ ማድረግ እንዳለባቸው በምሳሌያዊ መልኩ ለክርስቲያኖች ይናገራል፥
  • አንድ ሰው የኃጢአት ምርኮኛ መሆን ስለሚችልበት ሁኔታም ይናገራል፤ ይህም ኃጢአት፣ “ይቆጣጠረዋል” ማለት ነው።