am_tw/bible/other/camel.md

968 B

ግመል

ግመል ጀርባው ላይ አንድ ወይም ሁለት ሻኛ ያለው ግዙፍ ባለ አራት እግር እንስሳ ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ግመል በእስራኤልና በአካባቢው አገሮች የሚገኝ ትልቁ እንስሳ ነበር።
  • ግመል ሰዎችና ሌሎች ነገሮችን ለመሸከም በዋነኛነት ደረጃ ጥቅም ላይ ይውል ነበር።
  • አንዳንድ ሕዝቦች ግመልን ለምግብነትም ይጠቀሙበት የነበረ ቢሆንም፣ ግመል ንጹሕ ያልሆነ እንስሳ መሆኑንና መበላትም እንደሌለበት እግዚአብሔር በመናገሩ እስራኤላውያን ግን አይበሉትም ነበር።
  • በአሸዋ ላይ በፍጥነት መጓዝና ያለ ምግብ ውሃ ለበርካታ ሳምንቶች መኖር ይችል ስለ ነበር ግመል በጣም ጠቃሚ እንስሳ ነው።