am_tw/bible/other/bread.md

2.3 KiB

እንጀራ፣ ዳቦ

እንጀራ ውሃና ዘይት ተቀላቅሎ ከተቦካ ዱቄት ሊጥ ይሠራል። ከዚያ ሊጡ የእንጀራውን ወይም የዳቦውን ቅርጽ እንዲይዝ ተደርጎ ይጋገራል።

  • ብዙውን ጊዜ የእንጀራ ወይም የዳቦ ሊጥ ኩፍ እንዲል እርሾን የመሰለ ነገር ይገባበታል።
  • ኩፍ እንዳይል ከተፈለገ እንጀራን ወይም ዳቦን ያለ እርሾ ሊጋገር ይችላል። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲህ ያለው፣ “ያልቦካ እንጀራ” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ በፋሲካ ሰሞን አይሁድ የሚበሉት እንዲህ ያለውን እንጀራ ነው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን እንጀራ ወይም ዳቦ የብዙ ሰዎች ዋና ምግብ ሲሆን፣ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃሉ ማንኛውንም ምግብ ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል።
  • “ገጸ ኅብስት” የሚለው ቃል መገናኛው ድንኳን ወይም ቤተ መቅደስ ውስጥ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት እንዲሆኑ አሥራ ሁለት ኅብስቶች ወይም እንጀራዎች ወይም ዳቦዎች የወርቁ መሠዊያ ላይ ይቀመጡ ነበር። እነዚህ ኅብስቶች አሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶችን የሚወክሉ ሲሆን፣ የሚበሏቸው ካህናቱ ብቻ ነበሩ። ይህ ቃል፣ “እግዚአብሔር በመካከላቸው መሆኑን የሚያመለክቱ ኅብስቶች” ተብሎ መተርጎም ይችላል።
  • “ከሰማይ እንጀራ” የተሰኘው ምሳሌያዊ አነጋገር በምድረ በዳ በነበሩ ጊዜ እግዚአብሔር ለእስራኤል የሰጠውን፣ “መና” የሚባለውን የተለየ ነጭ ምግብ ያመለክታል።
  • ኢየሱስም፣ “ከሰማይ የወረደ እንጀራ” እና፣ “የሕይወት እንጀራ” በማለት ራሱን ጠርቷል።
  • ከመሞቱ በፊት ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ የፋሲካውን ምግብ አብረው እየበሉ በነበረ ጊዜ ያልቦካውን የፋሲካ እንጀራ መስቀል ላይ ከሚቆስለውና ከሚገደለው የራሱ አካል ጋር አመሳስሎት ነበር።