am_tw/bible/other/bold.md

1.4 KiB

ደፋር፣ በድፍረት፣ ድፍረት

እነዚህ ቃሎች አስቸጋሪና አደገኛ ቢሆን እንኳ እውነትን ለመናገርና ትክክለኛውን ለማድረግ ደፋርና ጎበዝ መሆንን ነው የሚያመለክቱት።

  • ደፋር ሰው ለተበደሉ መከራከርን ጨምሮ መልካምና ትክክል የሆነ ነገርን ለመናገር አይፈራም። ይህ፣ “ጎበዝ” ወይም “ፍርሃት የለሽ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።
  • ከአዲስ ኪዳን እንደምንመለክተው ለታሰሩ ወይም ሊገደሉ እንደሚችሉ ቢያውቁ እንኳ ደቀ መዛሙርት በአደባባይ ስለ ኢየሱስ፣ “በድፍረት” እውነቱን መናገራቸውን እንደ ቀጠለ እንመለከታለን። ይህ፣ “በልበ ሙሉነት” ወይም፣ “በጽናት” ወይም፣ “ያለ አንዳች ፍርሃት” ተብሎ መተርጎም ይችላል።
  • እነዚህን የጥንት ደቀ መዛሙርት የክርስቶስን መስቀል ላይ ሞት ቤዛነት የምሥራች “በድፍረት” ከመናገራቸው የተነሣ በእስራኤልና በአጎራባች አገሮች በመጨረሻም ወደ ተቀረው ዓለም ሁሉ ወንጌል ተስፋፋ። “ድፍረት” የሚለው ቃል፣ “የማያወላውል ጽናት” ተብሎ መተርጎም ይችላል።