am_tw/bible/other/beg.md

1008 B

መለመን፥ ለማኝ

“መለመን” አንድን ነገር አጥብቆ መጠየቅ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ገንዘብ ወይም እንጀራ መጠየቅን ይመለከታል።

  • “ለማኝ” ከሰዎች ገንዘብ ወይም እንጀራ ለመጠየቅ መንገድ ዳር የሚቀመጥ ወይም የሚቆም ወይም ከቦታ ቦታ የሚዘዋወር ሰው ነው
  • ብዙውን ጊዜ ሰዎች አጥብቀው አንድን ነገር ሲፈልጉ፥ ይለምናሉ፤ የለመኑት ነገር እንደሚሰጣቸው ግን አያውቁም። ይህ፥ “መወትወት” ወይም፥ “አጥብቆ መጠየቅ” ተብሎ መተርጎም ይችላል
  • የሚናገርው ገንዘብ ወይም እንጀራ መጠየቅን አስመልክቶ ከሆን፥ “ገንዘብ መጠየቅ” ወይም፥ “እንጀራ መጠየቅ” ወይም፥ “ዘወትር አንድን ነገር መጠየቅ” ተብሎ መተርጎምም ይቻላል።