am_tw/bible/other/bear.md

751 B

መሸከም

ቃል በቃል ከተወሰደ፣ “መሸከም” አንድን ነገር ራስ ላይ መጫን ማለት ነው። ይህ ቃል በርካታ ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት።

  • በማኅፀንዋ ልጅ የተሸከመች ሴት ያረገዘች ሴት ማለት ነው።
  • “ሸክም መሸከም” አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ማለፍ ማለት ነው። ይህ አስቸጋሪ ሁኔታ አካላዊ ወይም ስሜታዊ መከራ ሊሆን ይችላል።
  • “ልጅ የአባቱን ኀጢአት ይሸከማል” ማለት፣ “አባቱ ለፈጸመው ኀጢአት ኀላፊነት አለበት” ወይም፣ “በአባቱ ኀጢአት ይቀጣል” ማለት ነው።