am_tw/bible/other/armor.md

1.2 KiB

መሣሪያ

  • “መሣሪያ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንድ ወታደር በጦርነት የሚዋጋበትንና ከጠላት ጥቃት ራሱን የሚከለክልበትን ትጥቅ ነው። መንፈሳዊ መሣሪያን ለማመልከትም በምሳሌያዊ መንገድ ጥቅም ላይ ይውላል።
  • ከወታደሩ መሣሪያዎች ጥቂቶቹ የራስ ቁር፥ ጋሻ፥ ጥሩር፥ ጉልበት መሸፈኛና ሰይፍ ናቸው።
  • በምሳሌያዊ መንገድ ሲጠቀምበት ቁሳዊ መሣሪያን በመንፈሳዊ ውጊያ እንዲረዳው እግዚአብሔር ለአማኝ ከሰጠው መንፈሳዊ መሣሪያ ጋር ያነጻጽረዋል
  • ኅጢአትንና ሰይጣንን እንዲዋጉበት እግዚአብሔር ለሕዝቡ ከሰጣቸው መንፈሳዊ መሣሪያ አንዳንዶቹ እውነት፥ ጽድቅ፥ የሰላም ወንጌል፥ እምነት፥ ድነትና መንፈስ ቅዱስ ናቸው
  • ይህም፥ “የወታደሩ ማጥቂያ” ወይም “መከላከያ የጦር ልብስ” ወይም “መከለያ ሽፋን” ወይም እንዲሁ “ መሣሪያዎች” ተብሎ መተርጎም ይቻላል።