am_tw/bible/other/ambassador.md

1.7 KiB

እንደራሴ(አምባሳደር)፣ተወካይ

እንደ ራሴ(አምባሳደር)ሀገሩን በይፋ በመወከል ለውጪ አገሮች ጋር ግንኙነት እንዲያደርግ የሚመረጥ ሰው ነው፥ ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን አንዳንዴ ጠቅለል ባለ ሁኔታ፣ “ተወካይ” ተብሎም ይተረጎማል።

  • እንድ እንደ ራሴ ወይም ተወካይ ከላከው ሰው ወይም መንግስት ለሰዎች መልእክት ይሰጣል።
  • “ተወካይ” የተሰኘው ይበልጥ አጠቃላይ የሆነውን ቃል በሚወክለው ሰው ቦታ ሆኖ እንዲሠራ እንዲናገር ሥልጣን የተሰጠውን ሰው ያመለክታል።
  • በዚህ ዓለም ክርስቶስ የሚወክልና የእርሱን መልዕክት ለሌሎች የሚያስተምሩ በመሆናቸው ክርስቲያኖች የክርስቶስ፣ “እንደራሴዎች” ወይም “ተወካዮች” መሆናቸውን ሐዋርያው ጳውሎስ አስተምርሯል።
  • ጥቅም ላይ በዋለበት ዐውድ መሠረት ይህ ቃል፣ መንግሥታዊ ተወካይ ወይም፣የተሾመ መልእክተኛ ወይም “የመረጠ” ተወካይ ወይም፣በእግዚዘብሔር ተወካይ ተብሎ መተርጎም ይችላል።
  • “የእንደራሴዎች ቡድን” የሚለው፣ “ጥቂት መንግስታዊ መልዕክተኞች” ወይም፣ “የተመረጡ ተወካዮች ቡድን” ወይም ሰዎችን ሁሉ በመወከል ለሰዎች እንዲናገር ሥልጣን ያለው ቡድን ተብሎ መተርጎም ይቻላል።