am_tw/bible/other/alarm.md

1.1 KiB

ማስጠንቀቂያ/መሸበር

ማስጠቀቂያ የሚጎዳቸውን ነገር አስመልክቶ ሰዎችን ማሳሰብ ማስጠንቀቅ ማለት ነው።መሸበር አደገኛ ወይም ስጋት ያለውን ነገር በተመለከተ በጣም መጨነቅና መፍራት ማለት ነው።

  • ሞዓባውያን የይሁዳን መንግሥት ለማጥቃት እያቀዱ እንደ ነበር ሲሰማ ንጉሥ ኢዮሳፍጥ በጣም ተሸበረ።
  • በመጨረሻው ቀን ጥፋት እየደረሰ መሆኑን ሲሰሙ መሸበር እንደሌለባቸው ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ተናገረ።
  • “የማስጠንቀቂያ ደወል” የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር ማስጠንቀቅ ማለት ነው። በጥንት ዘመን ሰዎች መለከት ወይም ደወል የመሳሰሉ ነገሮችን ድምጽ በማሰማት የማስጠንቀቂያ ያስተላልፉ ነበር። የማስጠንቀቂያ ድምጽ ማሰማት ለሰዎች ስለ አደጋ መናገር እነርሱም ሌሎችን እንዲያስጠነቅቁ፥ ማድረግንም ይጨምራል።