am_tw/bible/other/acacia.md

886 B

ግራር

“ግራር” የተሰኘው ቃል በጥንት ዘመን በከነዓን ምድር ይበቅል የነበረው በብዛት ይገኝ የነበረው ቁጥቋጦ ወይም ዛፍ ስም ነው። ዛሬም ቢሆን በዚያ አካባቢ በብዛት ይገኛል።

  • ብርቱካናማ፣ ቡኒ መልክ ያለው የግራር እንጨት በጣም ጠንካራና ረጅም ዘመን መኖር የሚችል በመሆኑ አንዳንድ ነገሮችን ለመሥራት ያገለግላል።
  • ይህ እንጨት ውስጡ ውሃ የማይዝ ጥቅጥቅ ያለ በመሆኑ ለረዥም ዘመን አይበላሽም፤ምስጦችን የሚከላከል ተፈጥሮአዊ መከላከያ አለው።
  • በመጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን የግራር እንጨት የቃል ኪዳኑን ታቦ ለመሥራት ጥቅም ላይ ውሏል።