am_tw/bible/names/troas.md

878 B

ጢሮአዳ

የጢሮአዳ ከተማ በጥንቱ የሮም እስያ አውራጃ ሰሜን ምዕራብ ባሕር ዳርቻ ትገኝ የነበረች ወደብ ናት።

  • በሐዋርያዊ ጉዞው እግረ መንገዱን ጳውሎስ ቢያንስ ሦስት ጊዜ ወደ ጢሮአዳ መጥቶ ነበር።
  • አንድ ጊዜ እዚያ እያለ ጳውሎስ ስብከቱን እስከ ዕኩለ ሌሊት ድረስ በማርዘሙ አውጤኪስ የሚባል ወጣት አንቀላፋ። የተቀመጠው የተከፈተ መስኮት አጠገብ ስለ ነበር አውጤኪስ ወድቆ ሞተ። በእግዚአብሔር ኀይል ጳውሎስ ያንን ወጣት ከሞት አስነሣው።
  • ጳውሎስ ሮም በነበረ ጊዜ ጢሮአዳ ትቶት የመጣውን መጽሐፍና ካባ እንዲያመጣለት ለጢሞቴዎስ ተናገረ።