am_tw/bible/names/noah.md

994 B

ኖኅ

ኖኅ በዓለም የነበሩ ክፉ ሰዎችን ለማጥፋት እግዚአብሔር ዓለምን ሁሉ የሚያዳርስ ጎርፍ በላከበት ጊዜ ከ4000 ዓመት በፊት ይኖር የነበረ ሰው ነው። ጎርፉ ምድርን በሚሸፍንበት ጊዜ እርሱና ቤተ ሰቡ የሚኖሩበት ግዙፍ መርከብ እንዲሠራ እግዚአብሔር ለኖኅ ነገረው።

  • ኖኅ በማንኛውም ነገር ለእግዚአብሔር የታዘዘ ጻድቅ ሰው ነበር።
  • ግዙፉን መርከብ እንዴት እንደሚሠራ እግዚአብሔር ሲነግረው ኖኅ በትክክል እግዚአብሔር በነገረው መሠረት ሠራው።
  • መርከቡ ውስጥ ኖኅና ቤተ ሰቡ በመልካም ሁኔታ ነበር፤ በኋላም ልጆቹና የልጅ ልጆቹ ምድርን እንደ ገና በሰዎች ሞሉ።
  • ከጥፋት ውሃ በኋላ የተወለደ ሁሉ የኖኅ ቤተ ሰብ ነው።