am_tw/bible/names/nehemiah.md

1.3 KiB

ነህምያ

ነህምያ የእስራኤልና የይሁዳ ሕዝብ በባቢሎናውያን በምርኮኝነት በተወሰዱ ጊዜ ባቢሎን መንግሥት ውስጥ ይኖር የነበረ እስራኤላዊ ነው።

  • የፋርስ ንጉሥ የአርጤክስስ ወይን ጠጅ አሳላፊ በነበረ ጊዜ ነህምያ ወደ ባቢሎን ለመመለስ ከንጉሡ ፈቃድ ጠየቀ።
  • ባቢሎናውያን የደመሰሱትን የኢየሩሳሌም ቅጥር እንደ ገና እንዲሠራ እስራኤላውያንን የመራ ነህምያ ነበር።
  • ወደ ንጉሡ ቤተ መንግሥት ከመመለሱ በፊት ለአሥራ ሁለት ዓመት የኢየሩሳሌም አስታዳሪ ነበር።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ የምናገኘው መጽሐፈ ነህምያ የኢየሩሳሌምን ቅጥሮች ለመሥራትና ሕዝቡን ለማስተዳደር ነህምያ ያደረገውን ውጣ ውረድ ያቀርባል።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ነህምያ የሚባሉ ሌሎች ሰዎችም ነበር። ማንነታቸውን መለየት እንዲቻል በእነዚህ የተለያዩ ሰዎች ስም ጋር የአባታቸው ስም ተያይዞአል፤ ለምሳሌ፣ “የሐካልያ ልጅ ነህምያ” እንደሚለው።