am_tw/bible/names/mediterranean.md

1.0 KiB

ባሕሩ፣ ታላቁ ባሕር፣ የምዕራብ ባሕር

መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ታላቁ ባሕር” ወይም፣ “የምዕራብ ባሕር” የሚለው በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን የነበሩ ሰዎች ከሚያውቁት ባሕር ትልቁ የነበረው፣ ሜዲትራንያን ባሕርን ነው።

  • ታላቁ ባሕር (ሜዲትራንያን) ከእስራኤል፣ በሰሜንና በምዕራብ ከአውሮፓ፣ እና በሰሜን ከአፍሪካ ጋር ይዋሰናል።
  • ብዙ አገሮችን የሚያካልል በመሆኑ በጥንት ዘመን ይህ ባሕር ለንግድና ለጉዞ በጣም ጠቃሚ ነበር። ከሌሎች አገሮች ጋር በመርከብ በቀላሉ የንግድ ልውውጥ ማድረግ በመቻላቸው በዚህ ባሕር ዳርቻ የነበሩ ከተሞችና ሰዎች በጣም ሀብታም ነበር።
  • ታላቁ ባሕር የሚገኘው ከእስራኤል በስተ ምዕራብ በመሆኑ፣ “የምዕራብ ባሕር” ተብሏል።