am_tw/bible/names/marysisterofmartha.md

810 B

ማርያም (የማርታ እኅት)

ማርያም ቢታንያ በሚባል ቦታ ትኖር የነበረ የኢየሱስ ተከታይ ናት።

  • ማርያም ማርታ የምትባል እኅትና አልዓዛር የሚባል ወንድም ነበራት፤ ሁለቱም የኢየሱስ ተከታዮች ነበር።
  • ለእርሱ ምግብ ለማዘጋጀት ወዲያ ወዲህ ከማለት ይልቅ እርሱን መስማት ስለ መረጠች አንድ ጊዜ ኢየሱስ ማርያምን አመስግኗት ነበር።
  • አንድ ጊዜ ኢየሱስ በቢታንያ ምግብ ለመብላት ተቀምጦ እያለ፣ እርሱን ለማምለክ ማርያም ዋጋው ውድ የሆነ ሽቱ እግሩ ላይ አፈሰሰች፤ ይህን በማድረጓም ኢየሱስ አመስግኗታል።