am_tw/bible/names/manasseh.md

1.9 KiB

ምናሴ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ምናሴ ተብለው የተጠሩ አምስት ሰዎች ነበር።

  • ምናሴ የዮሴፍ መጀመሪያ ልጅ ስም ነው።
  • ምናሴንና ታናሽ ወንድሙ ኤፍሬምን የዮሴፍ አባት ያዕቆብ እንደ ገዛ ራሱ ልጆች ተቀብሎአቸዋል፤ በአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ውስጥ የመሆንን መብትም ሰጥቷቸዋል።
  • የምናሴ ነገድ ከእስራኤል ነገዶች አንዱ ሆኗል።
  • የምናሴ ነገድ ብዙውን ጊዜ፣ “የምናሴ ነገድ ዕኩሌታ” ተብሎ ተጠርቷል፤ ምክንያቱም ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተ ምዕራብ በምድረ ከነዓን የሰፈረው የነገዱ ግማሽ ብቻ ስለ ነበር ነው። የነገዱ ሌላው ግማሽ የሰረፈው ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተ ምሥራቅ ነበር።
  • ከይሁዳ ንጉሦች አንዱ ምናሴ ይባል ነበር።
  • ንጉሥ ምናሴ የገዛ ልጆቹን እንኳ ለሐሰተኛ አማልክት መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበ ክፉ ንጉሥ ነበር።
  • በጠላት ሰራዊት እጅ እንዲወድቅ በማድረግ እግዚአብሔር ንጉሥ ምናሴን ቀጣው። ምናሴ ወደ እግዚአብሔር በመመለስ ጣዖቶች ይመለኩባቸው የነበሩ መሠዊያዎች አፈራርሷል።
  • በዕዝራ ዘመን የነበሩት ምናሴ የሚል ስም የነበራቸው ሁለት ሰዎች ሁለቱም የባዕድ አገር ሴቶች አግብተው ነበር። ባዕዳን አምልኮቶቻቸው ካሳደሩት ተፅዕኖ የተነሣ እነዚህ ሰዎች ሚስቶቻቸውን እንዲፈቱ ተጠይቀው ነበር።
  • ሌላው ምናሴ የተባለው ሰው የሐሰተኛ አማልክት ካህናት የነበሩ የዳን ወገኖች አያት ነበር።