am_tw/bible/names/johnthebaptist.md

957 B

ዮሐንስ (መጥምቁ)

ዮሐንስ የዘካርያስና የኤልሳቤጥ ልጅ ነበር። ዮሐንስ የተሰኘው ስም በጣም የተለመደ ከመሆኑ የተነሳ ሐዋርያው ዮሐንስን ከመሳሰሉ ዮሐንስ ከተባሉ ሌሎች ሰዎች እርሱን ለመለየት፣ “መጥምቁ ዮሐንስ” ተብሏል።

  • ዮሐንስ በእርሱ እንደሚያምኑና መሲሑን እንዲከተሉ ሰዎችን ለማዘጋጀት እግዚአብሔር የላከው ነቢይ ነበር።
  • መሲሑን ለመቀበል ዝግጁ ለመሆን ኀጢአታቸውን እንዲናዘዙ፣ ወደእግዚአብሔር እንዲመለሱና ኀጢአትን እንዲተው ዮሐንስ ለሕዝቡ ነገረ።
  • በኀጢአታቸው ለመጸጸታቸውና ከኀጢአታቸው ፊታቸውን ለማዞራቸው ምልክት እንዲሆን ዮሐንስ ብዙ ሰዎችን በውሃ አጠመቀ።