am_tw/bible/names/job.md

1.4 KiB

ኢዮብ

ኢዮብ፣ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅና በደል የሌለበት እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገርለት ሰው ነው። የበለጠ የሚታወቀው ታላቅ ስቃይና ሐዘን ቢደርስበትም በእግዚአብሔር በነበረው እምነት በመጽናቱ ነበር።

  • ኢዮብ በዚህ ምድር የነበረው ዓለምን ሁሉ ካደረሰው የኖኅ ዘመን ጎርፍ በኋላና አብርሃም ከነበረበት ዘመን በፊት እንደነበር ይታሰባል።
  • ኢዮብ በሞተበት ጊዜ ዕድሜው ምናልባት ሁለት መቶ ዓመት ሳይሆን አይቀርም።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለው መጽሐፈ ኢዮብ በሕይወቱ ከደረሱት አያሌ አውዳሚ ሁኔታዎች የተነሣ ኢዮብ ላይ ስለ ደረሰው መከራ ይናገራል። የአጽናፍ ዓለሙ ሉዓላዊ ፈጣሪ እንደመሆኑ መጠን ነገሮችን ከእግዚአብሔር ዕይታ አንጻር ከማቅረብም በላይ ያንን መከራ በተመለከት ኢዮብና ሌሎች ሰዎች ስለሰጡት ምላሽም ይናገራል።
  • ከዚያ ሁሉ ውድመት በኋላ መጨረሻ ላይ እግዚአብሔር ሁሉንም እንደገና ለኢዮብ መለሰለት፤ እርሱንና ቤተሰቡን በሀብት በጣም ባረካቸው።