am_tw/bible/names/jamessonofzebedee.md

830 B

ያዕቆብ (የዘብዴዎስ ልጅ)

የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር። ዮሐንስ የሚባል ታናሽ ወንድም የነበሩት ሲሆን፣ እርሱም ከኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር።

  • ያዕቆብና ዮሐንስ፣ “የነጎድጓድ ልጆች” የተሰኘ መጠሪያ ነበራቸው፤ እንዲህ የተባሉት ምናልባት ቶሎ ስለሚቆጡ ሊሆን ይችላል።
  • ይኸኛው ያዕቆብ፣ የያዕቆብ መልእክትን ከጻፈው የተለየ ነው። ሁለቱ የተለያዩ ሰዎች መሆናቸውን ለማመልከት አንዳንድ ቋንቋዎች ስሞቻቸውን በተለየ ሁኔታ መጻፍ የሚችሉበት መንገድ ይኖራቸዋል።