am_tw/bible/names/jamesbrotherofjesus.md

711 B

ያዕቆብ (የኢየሱስ ወንድም)

ያዕቆብ የማርያምና የዮሴፍ ልጅ ሲሆን፣ ከኢየሱስ ግማሽ ወንድሞች አንዱ ነበር።

  • ኢየሱስ በዚህ ምድር በነበረ ጊዜ እርሱ መሲሕ መሆኑን ያዕቆብና ወንድሞቹ አላመኑም ነበር።
  • ኢየሱስ ከሞት ከተነሣ በኋላ ግን ያዕቆብ በእርሱ አምኗል፤ በኢየሩሳሌም የነበረችው ቤተ ክርስቲያንም መሪ ሆኗል።
  • ያዕቆብ በሌሎች አገሮች ለነበሩ ክርስቲያኖች መልእክት ጽፎአል። መልእክቱም፣ “የያዕቆብ መልእክት” ተብሎ ይታወቃል።