am_tw/bible/names/jacob.md

1.1 KiB

ያዕቆብ፣ እስራኤል

ያዕቆብ የይስሐቅና የርብቃ ታናሹ መንታ ልጅ ነው።

  • ያዕቆብ፣ “አታላይ” ወይም፣ “አሳሳች” ማለት ነው።
  • ያዕቆብ ብልጥና አታላይ ነበር። በአታላይነቱ የበኩር ልጅነትን ውርስ እና የታላቅ ወንድሙ የኤሳውን በረከት መውሰድ ችሏል።
  • ኤሳው በጣም ተቆጥቶ ያዕቆብን መግደል ፈለገ፤ ስለዚህ ያዕቆብ የትውልድ ቦታውን ለቅቆ ሸሸ። በኋላ ግን ተመልሶ ከወንድሙ ጋር በሰላም ኖሮአል።
  • የያዕቆብን ስም እግዚአብሔር እስራኤል ወደሚል ለወጠው፣ ያም፣ “ከእግዚአብሔር ጋር ታገለ” ማለት ነው።
  • የአብርሃም ልጆች በሆኑት በይስሐቅና በልጁ በያዕቆብ በኩል እግዚአብሔር ለአብርሃምና ለዘሮቹ የገባውን ኪዳን ፈጸመ።
  • ያዕቆብ አሥራ ሁለት ልጆች ነበሩት። የእነርሱ ዘሮች አሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ሆነዋል።