am_tw/bible/names/hamath.md

1.1 KiB

ሐማት፣ ሌቦ ሐማት

ሐማት ከምድረ ከነዓን በስተ ሰሜናዊ ሶርያ ውስጥ ትገኝ የነበረች በጣም ጠቃሚ ከተማ ናት። በዚህ ዘመን የከተማዋ ስም ሐማ ይባላል።

  • “ሌቦ ሐማት” የሚለው ቃል ሐማት ከተማ አጠገብ የሚገኝ የተራራ መሻገሪያን የሚያመለክት ሊሆን ይችላል።
  • አንዳንድ ትርጕሞች “ሌቦ ሐማት” የሚለውን፣ “ወደ ሐማት መግቢያ” ብለውታል።
  • “ሐማታውያን” የኖኅ ልጅ የካምና የልጅ ልጁ የከነዓን ዘሮች ናቸው።
  • ንጉሥ ዳዊት የሐማት ንጉሥ የቶዑን ጠላቶች ድል በማድረጉ በሁለቱ መካከል ወዳጅነት ተመሠረተ።
  • ሐማት አስፈላጊ ነገሮች የሚከማቹበት ከንጉሥ ሰሎሞን ግምጃ ቤት ከተሞች አንዷ ነበረች።
  • ንጉሥ ሴዴቅያስ በንጉሥ ናቡከደነፆር የተገደለውና ንጉሥ ኢዮአካዝ በግብፃዊው ፈርዖን የተያዘው በሐማት ምድር ነበር።